Saturday, December 21, 2019

ሶማሊያዊያን የአንበጣውን መንጋ ለምግብነት በማዋል እየተዋጉት ነው

አንበጣ ለምግብነት ሲዘጋጅበሰሜናዊ የኢትዮጵያ ክፍል እንደተስተዋለው ሁሉ ጎረቤት ሃገር ሶማሊያም በ25 ዓመታት ውስጥ አይታ የማታውቀው ከፍተኛ የአንበጣ መንጋ ወረራ አጋጥሟታል።
በሃገራችን የአንበጣውን መንጋን ከፍተኛ ድምጽ በማውጣት ነበር ህዝቡ ከአካባቢው ሲያባረው የቆየው።
የጎረቤት ሃገር ሶማሊያ ዜጎች ግን መፍትሄ ያሉትን ሌላ መላ ዘይደዋል። ይህም፤ የአንበጣ መንጋውን መያዝ፣ በውሃ መዘፍዘፍ፣ አጠንፍፎ በዘይት ጠብሶ መመገብ።
በሶማሊያ አዳዶ ከተማ የሚገኙ ነዋሪዎች አንበጣን ጠብሰው ከሩዝ እና ከፓስታ ጋር ለምግብነት እያዋሉት ነው።
አንዱ የከተማዋ ነዋሪ "አንበጣው ከአሳ በላይ ልዩ ጣዕም አለው" ያለ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ የአንበጣው የንጥረ ነገር ይዘት ፍቱን የሆነ መድሃኒት እንደያዘ እንደሚያምን ይናገራል።
ይሄው ግለሰብ ዩኒቨርሳል ሶማሊያ ለተሰኘ የቴሌቪዥን ጣቢያ አስተያየቱን ሲሰጥ፤ አንበጣው ውስጥ የሚገኘው ንጥረ ነገር የደም ግፊቱን እንደሚያስተካክልለት እና የጀርባ ህመሙን እንደሚያሽልለት ተስፋ አድርጓል።

No comments:

Post a Comment